ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በባልደረቦቻቸው መሀል ተቀምጠው ሳለ እንዲህ አሉ፦ "ይህ ወቅት እውቀት ከሰዎች የሚነጠቅና የሚነሳበት ወቅት ነው።" ይህኔ ዚያድ ቢን ለቢድ አልአንሷሪይ በመደነቅ ነቢዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ጠየቁ። እንዲህም አሉ፦ "ቁርኣንን ቀርተነዋል፣ በቃላችን ሸምድደነዋል በአላህ እምላለሁ! እንቀራዋለን፣ ሴቶቻችንንም ልጆቻችንንም፣ የልጅ ልጆቻችንንም እያስቀራነው እንዴት ዕውቀት ይነሳል ከኛ እንዴት ይጠፋል?!" ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በመደነቅ እንዲህ አሉ: "ዚያድ ሆይ! እናትህ ትጣህና ከመዲና ነዋሪዎች ውስጥ ከሚገኙ ዐሊሞች እቆጥርህ ነበርኩ።" ከዚያም ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ለሱ ዕውቀት የሚጠፋው ቁርኣን በመጥፋቱ እንዳልሆነ ነገር ግን ዕውቀት የሚጠፋው በዕውቀት መሥራት ሲጠፋ እንደሆነ አብራሩለት። ተውራትና ኢንጂል አይሁዶችና ክርስቲያኖች ዘንድ አለ። ከዚህም ጋር ምንም አልጠቀማቸውምም የታለመለትንም ግብ አላሳኩም። የታለመለት ዓላማ ባወቁት መሥራት ነበርና።