ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ጀናዛ ቃሬዛ ላይ የተቀመጠ ጊዜና ሰዎችም ትከሻቸው ላይ የተሸከሟት ጊዜ መልካም ከሆነች ከፊት ለፊቷ ፀጋዎችን ስለምትመለከት "ቀደም አድርጉኝ!" ትላለች። መልካም ካልሆነች ደግሞ ከፊት ለፊቷ ቅጣትን ስለምትመለከት በሚያወግዝ ድምፅ "ወይ ጥፋቷ! የት ነው ይዛችኋት የምትሄዱት?!" ትላለች። ከሰው በቀር ሁሉ ነገር ድምጿን ይሰማታል። ሰው ቢሰማው ኖሮ የሚሰማው ነገር ከባድ ከመሆኑ የተነሳ ራሱን ይስት ነበር አሉ።