አማኝ ቀብር ውስጥ ይጠየቃል። ለዚህ ስራ የተወከሉ ሁለት መላእክት ይጠይቁታል። እነሱም በበርካታ ሐዲሦች ስማቸው እንደተጠቀሰው ነኪርና ሙንከር ናቸው። ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለና ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን ይመሰክራል። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ይህ ነው አላህ የተረጋገጠው ቃል ብሎ የተናገረበት አሉ: {አላህ እነዚያን ያመኑትን በቅርቢቱም ህይወት በመጨረሻይቱም (በመቃብር) በተረጋገጠው ቃል ላይ ያረጋቸዋል።} [ኢብራሂም:27]