ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በመጨረሻዎቹ ኡመታቸው ውስጥ ውሸትን የሚቀጥፉ ሰዎች ብቅ እንደሚሉ ተናገሩ። ከነርሱ በፊት አንድም ሰው ያልተናገረውን ይናገራሉ፤ የተዋሹና የተቀጠፉ ሐዲሦችን ይናገራሉ። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከነርሱ እንድንርቅና እንዳንቀማመጣቸው፣ ከርሱ መራቅ እስኪያቅተን ድረስ ይህ የተቀጠፈ (የተፈበረከ) ሐዲሥ ነፍስ ውስጥ ተፅዕኖ እንዳያሳድርብንም ሐዲሣቸውን አለመስማትን አዘዙን።