ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ከእስልምና በፊት የቁረይሽ ሹማምንቶች መካከል ስለነበረው ዐብደላህ ቢን ጁድዓን ተናገሩ። ከመልካም ሥራዎቹ መካከልም፦ ዝምድናውን የሚቀጥል፣ ለነሱ መልካም የሚሰራ፣ ሚስኪኖችን የሚመግብና ሌሎችም እስልምና እንዲተገበር ያነሳሳቸውን መልካም ስራዎች የሚሰራ ነበር። እነዚህ ተግባሮቹ ግን በአላህ በመካዱና አንድ ቀንም "ጌታዬ ሆይ! የምንዳው ቀን ለኔ ወንጀሎቼን ማረኝ" ባለማለቱ ምክንያት ለመጪው ዓለም አትጠቅመውም።