አንድ ሰውዬ ወደ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዘንድ በመምጣት የግሉን ጉዳይ አወራቸውና ከዚያም "የአላህና የእርሶ መሻት ሆነ።" አላቸው። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ይህ ንግግሩን አወገዙት። የፍጡርን መሻት ከአላህ መሻት ጋር አቆራኝቶ መናገር ሙስሊም ሊለው የማይፈቀድለት ትንሹ ሺርክ መሆኑን ተናገሩ። ቀጥለውም ትክክለኛው አባባል "የብቸኛው አላህ መሻት ሆነ።" ማለቱ እንደሆነ ጠቆሙት። አላህን በመሻቱ መነጠል እንጂ በማንኛውም ማቆራኛ ቃላት የአንድንም አካል መሻት ከአሏህ ጋር ማቆራኘት የለበትም።