ከአቡ በሺር አል አንሷሪይ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው: እርሱ በአንድ ጉዞ ላይ ከአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ጋር ነበርና እንዲህ አለ: "ሰዎች በማደሪያቸው ባሉበት የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም (ይህንን የሚያውጅ) አንድ መልክተኛ ላኩ ' በግመል አንገት ላይ (የታሰረ) የቀስት ገመድ ወይም ገመድ የተቆረጠ ቢሆን እንጂ ምንም እንዳይቀር!'" ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አንድ ጉዞ ላይ ሰዎች በሚያድሩበት የግመልና የመኝታ ድንኳናቸው ስፍራቸው ውስጥ ባሉበት ወደ ሰዎች በግመል ላይ የምትንጠለጠል ገመድ እንድትቆረጥ የሚያዝ አንድን ሰው ላኩ። ይህም የቀስት ገመድም (ወተር) ይሁን ወይም ከርሱ ውጪ የቃጭልና የጫማ ገመድ የመሳሰሉም ቢሆን ተመሳሳይ ነው። ይህም የሰው አይን ፈርተው ያስሩት ስለነበር ነው። እንዲቆርጡት የታዘዙበት ምክንያትም ከነርሱ ላይ አንዳችም ነገር ስለማይመልስ ነው። ጥቅምና ጉዳት አጋር በሌለው በአላህ እጅ ብቻ ነውና።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • የቀስት ገመድና ማንኛውንም ገመድ ጥቅም ያመጣል ወይም ጉዳት ይከላከላል በሚል ማሰር ከሺርክ የሚመደብ ስለሆነ ክልክል ነው።
  • ከቀስት ገመድ ውጪ ያሉ ገመዶችን ማሰር ለውበት ወይም እንስሳን ለመምራት ወይም በርሱ ለማሰር ከሆነ ችግር የለውም።
  • መጥፎን በቻሉት መጠን ማውገዝ ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።
  • ልብን አጋር በሌለው አላህ ላይ ብቻ ማንጠልጠል ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።