ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በአብዛኛው ሰዎችን ጀነት ስለሚያስገባው ነገር ተጠየቁ፤ እሳቸውም "አላህን መፍራት እና መልካም ስነምግባር ነው።" አሉ። በአብዛኛው ሰዎችን እሳት ስለሚያስገባቸው ነገርም ተጠየቁ። እሳቸውም "ምላስና ብልት ነው።" አሉ። ሐሰኑን ሶሒሕ ነው። - ቲርሚዚ፣ ኢብኑ ማጀህና አሕመድ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ጀነት የሚያስገቡ ትልልቅ ምክንያቶች ሁለት መሆናቸውን ገለፁ። እነሱም: አላህን መፍራትና መልካም ስነምግባር ናቸው። አላህን መፍራት: በአንተና በአላህ ቅጣት መካከል መጠበቂያ ማድረግህ ነው። ይህም ትእዛዙን በመፈፀምና ክልከላውን በመራቅ ነው። መልካም ስነምግባር ደግሞ: ፊትን ፈታ በማድረግ ፣ መልካምን በመለገስና ፍጡራንን ከማወክ በመቆጠብ ነው። እሳት የሚያስገቡት ትልልቅ ምክንያቶች ደግሞ ሁለት ናቸው። እነሱም: ምላስና ብልት ናቸው። ከምላስ ወንጀሎች መካከል:- ውሸት፣ ሀሜት፣ ወሬ ማዋሰድና ሌሎችም ናቸው። ከብልት ወንጀሎች መካከል ደግሞ:- ዝሙት፣ ግብረሰዶምና ሌሎችም ይጠቀሳሉ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ጀነት መግባት ከአላህ ትእዛዝ ጋር የተገናኙ ምክንያቶች አሉት። ከነሱም መካከል:- አላህን መፍራትን ይጠቀሳል። ከሰዎች ጋር የተገናኙ ምክንያቶችም አሉት። ከነሱም መካከል:- መልካም ስነምግባር ይጠቀሳል።
  • ምላስ እሳት ከሚያስገቡ ምክንያቶች መካከል አንዱ ስለሆነ በባለቤቱ ላይ አደገኛ መሆኑን እንረዳለን።
  • የስሜት ተገዢ መሆንና ፀያፍ ወንጀሎችን መስራት በአብዛኛው እሳት የመግቢያ ምክንያቶች መካከል አንዱ ስለሆነ በሰው ላይ አደጋ መሆኑን እንረዳለን።