ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እውነተኝነትን አዘዙ። እውነተኝነትን አጥብቆ መያዝ ለዘውታሪ መልካም ስራና በመልካም ስራ ላይም እንዲዘወትር የሚያደርገው በመሆኑ ሰውዬውን ወደ ጀነት እንደሚያደርሰው ተናገሩ። ሰውዬው እውነት መናገርን በድብቅም ይሁን በይፋ ከመደጋገም እስካልተወገደ ድረስ እጅግ እውነተኛ የሚል ስያሜ ይሰጠዋል። ይህም በእውነተኝነት ላይ ጫፍ የደረሰ ሰው ማለት ነው። ቀጥለውም ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከውሸትና ከቅጥፈት ንግግር አስጠነቀቁ። ይህም ከቀጥተኛው መንገድ ወደ መጣመም፣ ለክፋትና ለወንጀል ስለሚያነሳሳ ነው። ከዚያም ወደ እሳት ያደርሰዋል። ሰውዬውም ውሸትን ከማብዛት እስካልተወገደ ድረስ አላህ ዘንድ ውሸታም ተብሎ ይፃፋል።