አላህ ዐዘ ወጀል ነቢዩን (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) የላካቸው መልካምና በላጭ ስነምግባርን ሊሞሉ እንደሆነ ተናገሩ። ይህም ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከርሳቸው በፊት የነበሩ መልክተኞች ላስተላለፉት የመልካምነት ጥሪ አሟይና ዐረቦች የነበሩበትን መልካም ስነምግባር ሊሞሉ ነው የተላኩት። ዐረቦች መልካምን የሚወዱና መጥፎን የሚጠሉ፣ የክብር፣ የቸርነትና የታላቅነት ባለቤት ነበሩ። ታዲያ ነቢዩም (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ዐረቦች የጎደላቸውን ስነምግባር ሊሞሉ ተላኩ። ለምሳሌ በዘር መኩራራት፣ ኩራት፣ ድሃን መናቅና ከዚህም ውጪ የሚጎድላቸው ስነምግባሮች ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው።