ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መስራቱ ሺርክ የሆኑ ነገሮችን ገለፁ። ከነሱም መካከል: - አንደኛ: ማነብነብ (ሩቃ) :- ይህም የጃሂሊያ ሰዎች ይታከሙበት የነበረውን ሽርክን የሰበሰበ ንግግር ነው። ሁለተኛ: በጨሌና በመሳሰሉ የተሰሩ ሂርዞችን ማንጠልጠል: ይህም የሰው አይን እንዲከላከል በህፃናት፣ በእንስሶችና በሌሎችም ላይ የሚንጠለጠል ነው። ሶስተኛ: መስተፋቅር: ይህም ከሁለቱ ጥንዶች መካከል አንዱ ሌላኛውን እንዲያፈቅር ተደርጎ የሚሰራ ነው። እነዚህ ነገሮች ከሺርክ የሚመደቡ ናቸው። ምክንያቱም ይህ በማስረጃ የፀና ሸሪዓዊ ሰበብም ያልሆነን በተለምዶ የተረጋገጠ ህዋሳዊ ሰበብም ያልሆነን ሰበብ አድርጎ መያዝ ነውና። እንደ ቁርአን መቅራት የመሰለ ሸሪዐዊ ሰበቦችን መጠቀም ወይም በተለምዶ የተረጋገጡ መድሃኒቶችን የመሰለ ህዋሳዊ ሰበቦችን መጠቀም ግን መጥቀምና መጉዳት በአላህ እጅ መሆኑንና እነሱ ሰበብ ብቻ መሆናቸውን ከማመን ጋር እስከሆነ ድረስ መጠቀም ይፈቀዳል።