አንድ ሰው ወደ ነቢዩየአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በመምጣት እንዲህ አለ፦ "የአላህ መልክተኛ ሆይ! እኔ ሁሉንም ዓይነት ወንጀሎችና ኃጢኣቶች ሰርቻለሁ፤ ትንሽም ሆነ ትልቅ ወንጀል ከመስራት አልተቆጠብኩም፤ ምህረት ይደረግልኝ ይሆን?" ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ለሱ "ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለ ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን ትመሰክር የለምን?" አሉት። ሶስት ጊዜ ደጋግመው ጠየቁት። እርሱም፦ "አዎን እመሰክራለሁ" በማለት መለሰላቸው። ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በሁለቱ የምስክር ቃላቶች ትሩፋትና ወንጀል የማስማር አቅማቸው እንደሚማር ነገሩት። ተውበት ያለፈውን ወንጀል ያብሳልና።