አንድ አይነ ስውር ሰውዬ ወደ ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በመምጣት "የአላህ መልክተኛ ሆይ! እኔ ዘንድ ለአምስቱ ሶላቶች እጄን ይዞ ወደ መስጂድ የሚወስደኝና የሚያግዘኝ የለም።" አለ። ፍላጎቱ ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ጀማዓን በመተው ለርሱ እንዲያግራሩለት ነው። ለርሱም አግራሩለት። ለመሄድ የዞረ ጊዜም ጠሩትና "የሶላትን አዛን ትሰማለህን?" አሉት። እርሱም "አዎን" አለ። እሳቸውም "የሶላቱን ተጣሪ ጥሪ መልስ" አሉት።