ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ነጭ ሽንኩርት ወይም ቀይ ሽንኩርት የበላ ሰው የጀማዓ ሶላት የሚገኙ ወንድሞቹን በጠረኑ እንዳያውክ መስጂድ ከመምጣት ከለከሉት። ይህ መስጂድ ከመምጣት የመጣው ክልከላ ግን የውግዘት ክልከላ ነው። መብላቱ የሚፈቀድ ምግብ ስለሆነ ክልከላው ከመብላት አይደለም። ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አረንጓዴ አትክልት ያለበት ድስት መጣላቸው። ከድስቱ ውስጥም ጠረንን ባሸተቱ ጊዜና ውስጡ ያለው ነገር ምንነቱ ሲነገራቸው ከመብላት ተቆጥበው አንዱ ባልደረባቸው እንዲበላ አቀረቡለት። ሰውዬውም እርሳቸውን ተከትሎ መብላቱን ጠላ። ነቢዩም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሰውዬውን የተመለከቱት ጊዜ እንዲህ አሉት: "ብላ! እኔ ያልበላሁት በራእይ ከመላእክት ጋር ስለምንሾካሾክ ነው።" ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የሰው ልጆች በመጥፎ ሽታ እንደሚታወኩት መላእክትም ይታወካሉ በማለት ተናገሩ።