ከዐብደላህ ቢን ዑመር ረዲየሏሁ ዐንሁማ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- የአስለሚዩን ሰውዬ በድንጋይ ወግረው ከገደሉ በኋላ ተነስተው እንዲህ አሉ: "አላህ ከርሱ የከለከለውን ይህን ቆሻሻ ድርጊት ራቁ። ይህን ድርጊት ከፈፀመም አላህ (ወንጀሉን) እንደሸሸገለት ይሸሽገው፤ ወደ አላህም ይመለስ። ወንጀሉን ለኛ ግልፅ የሚያደርግ ሰውም በአላህ መጽሐፍ መሰረት (ቅጣቱን) እንፈፅምበታለን።" ሶሒሕ ነው። - رواه الحاكم والبيهقي
explain-icon

ትንታኔ

ኢብኑ ዑመር ረዲየሏሁ ዐንሁማ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ማዒዝ ቢን ማሊክ አልአስለሚይን ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - በዝሙት ቅጣት በድንጋይ ወግረው ከገደሉት በኋላ ተነሱና ለሰዎች ኹጥባ አደረጉ። እንዲህም አሉ: አላህ የከለከላቸው የሆኑትን እነዚህን ቆሻሻ፣ ፀያፍና አስቀያሚ ወንጀሎች ራቁ። ከነዚህ ወንጀሎች አንዳችን የፈፀመ ካለም ሁለት ነገር መፈፀም ይጠበቅበታል: የመጀመሪያው: አላህ ወንጀሉን እንደሸሸገለት ተሸሽጎ ወንጀሉን አለመናገር። ሁለተኛው: ወደ አላህ ተውበት በማድረግ መቻኮል፣ በርሱ ላይ አለመዘውተር ነው። ወንጀሉ ለኛ ግልፅ የሆነችበት ሰው በርሱ ላይ በአላህ መጽሐፍ መሰረት ለዚህች ወንጀሉ የተጠቀሰውን ቅጣት እንፈፅምበታለን።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ወንጀለኛ የሆነ ሰው ነፍሱን በመሸሸግ ላይና በርሱና በጌታው መካከል ካሉ ወንጀሎች ተውበት በማድረግ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  • የሚያስቀጡ ወንጀሎች መሪ ዘንድ የደረሱ ጊዜ የግድ ቅጣቱን ተፈፃሚ ማድረግ እንዳለበት እንረዳለን።
  • ወንጀሎችን መራቅና ለወንጀሎች ተውበት ማድረግ ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።