ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አላህ አንዳንድ ባሮቹን እንደሚወድ ገለፁ። ከነርሱም መካከል ፈሪሃ አላህ የሆነ አንዱ ነው። እርሱም:- የአላህን ትእዛዛት የሚተገብርና ክልከላዎቹን የሚርቅ ነው። ከሰዎች የተብቃቃንም ይወዳል። እርሱም:- በአላህ በመመካቱ የተነሳ ከሰዎች የተብቃቃና ከአላህ ውጪ ወደ ማንም የማይዞር ነው። ድብቅንም ይወዳል። እርሱም:- ለጌታው ባሪያና የሚተናነስ፣ በሚጠቅመው ነገር ላይ የሚጠመድ፣ ማንም እርሱን ማወቁም ይሁን ስለርሱ በሙገሳና ውዳሴ ማውራቱን ከቁብ የማይቆጥር ሰው ነው።