explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አንድ ሰው ቁርአንን በልቡ ከሸመደደው በኋላ እንዳይረሳው ቁርአንን በመጠባበቅና በማንበቡ ላይ መዘውተርን አዘዙ። ቁርአን ከልብ ውስጥ ከታሰረች ግመል የበለጠ እጅግ የሚጠፋና የሚወገድ መሆኑን ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በመሀላቸው በማጠናከር ገለፁ። ግመል በክንዶቿ መሀል በገመድ ተጠፍራ ስታበቃ ሰውዬው ከተጠባበቃት ይይዛታል፤ ከለቀቃት ግን ትሄዳለችም ትጠፋለችም።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ቁርአንን የሸመደደ ሰውም ቁርአንን በማንበቡ ላይ በየጊዜው ከዘወተረ ልቡ ውስጥ እንደተጠበቀ ይቀራል። ያለበለዚያ ግን ይጠፋበታልም ይረሳዋልም።
  • ቁርአንን ከመጠባበቅ ጥቅሞች መካከል ምንዳና አጅርን ማግኘትና የትንሳኤ ቀን ከፍተኛ ደረጃን መጎናፀፍ ነው።