ከዐብደላህ ቢን መስዑድ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድለላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል: 'ከአላህ መጽሐፍ አንዲትን ፊደል የቀራ ሰው ለርሱ አንዲት ምንዳ ይሰጠዋል። አንዲት ምንዳ ደግሞ በአስር አምሳያዋ (ትባዛለች።) (ይሄንን ስል) {አሊፍ ላም ሚም} አንድ ፊደል ነው እያልኩ አይደለም። ነገር ግን {አሊፍ} አንድ ፊደል ነው። {ላም} አንድ ፊደል ነው። {ሚም} አንድ ፊደል ነው።'" ሶሒሕ ነው። - ቲርሚዚ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ማንኛውም ከአላህ መጽሐፍ አንድ ፊደል የሚቀራ ሙስሊም ለርሱ ምንዳ እንዳለውና አንዱ ምንዳ ደግሞ ለርሱ በአምሳያው እስከ አስር ድረስ እንደሚባዛለት ተናገሩ። ከዚያም ይህንን ({አሊፍ ላም ሚም} አንድ ፊደል ነው እያልኩ አይደለም። ነገር ግን {አሊፍ} አንድ ፊደል ነው። {ላም} አንድ ፊደል ነው። {ሚም} አንድ ፊደል ነው።) በሚለው ንግግራቸው ሶስት ፊደል እንደሚሆኑና ሰላሳ ምንዳ እንደሚሆኑ ገለፁ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ቁርአን ማንበብ በማብዛት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  • አንድ ቁርአን አንባቢ የሚያነባቸው ሁሉም ቃላት ውስጥ የሚገኙ ፊደላት በአስር አምሳያቸው የሚባዙ የሆኑ ምንዳዎች አሉት።
  • አላህ ለባሮቹ በራሱ ቸርነት ምንዳዎችን ማባዛቱ የርሱ እዝነትና ቸርነት ሰፊ መሆኑን ያስረዳናል።
  • ቁርአን ከሌሎች ንግግሮች በላይ ያለውን ብልጫና ማንበቡም አላህን ማምለኪያ መሆኑን እንረዳለን። ይህም እርሱ የአላህ ቃል ስለሆነ ነው።