explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በሁሉም ዓለማዊም ይሁን ዲናዊ በሆኑ ጉዳዮች ለሰዎች ማቅለልና ማግራራትን እንዲሁም እነርሱ ላይ አለማክበድን አዘዙ። ይህም ማግራራት አላህ በፈቀደውና በደነገገው ድንበር ውስጥ ሆኖ ነው። ሰዎችን በመልካም ነገሮች በማበሰርና እነርሱን ከመልካም ነገሮች ባለማሸሽ ላይም አበረታቱ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • የአንድ አማኝ ግዴታ ሰዎች አላህን እንዲወዱ ማድረግና በመልካም ነገሮች ላይ ማነሳሳት ነው።
  • ወደ አላህ የሚጣራ ሰው የኢስላምን ጥሪ ወደ ሰዎች በጥበብ እንዴት እንደሚያደርስ ማስተዋል ይገባዋል።
  • ማበሰር ለዳዒውም ለሚያስተላልፈው ነገርም ደስታን ተሰሚነትንና መረጋጋትን ያስተርፋል።
  • ማካበድ በዳዒው ንግግር ውስጥ ማሸሽን ፣ ተቀባይነት ማጣትና ጥርጣሬን ይፈጥራል።
  • ለነርሱ የወደደላቸው ገር እምነትና ቀላል ድንጋጌ በመሆኑ አላህ በባሮቹ ላይ ያለው እዝነት ሰፊ መሆኑን እንረዳለን።
  • እንድናግራራ የታዘዝንባቸውን ነገሮች ማግራራት ሸሪዓ ይዞት የመጣው አንዱ ድንጋጌ ነው።