ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ለባልደረቦቻቸው ኹጥባ ለማድረግ ተነሱ። ከተናገሯቸው መካከልም: አላህ እንዲህ ብሎ ራዕይ ማውረዱን ተናገሩ: ሰዎች በዘራቸው ወይም በገንዘባቸው ወይም ከዛ ውጪ ባሉ ነገሮች አንዱ በአንዱ ላይ ልቅናን፣ ኩራትንና ክብርን ለራሱ በማድረግ ሳይፎክርና አንዱ በአንዱ ላይ ወሰን ሳይተላለፍ ለፍጥረታት ራሳቸውን ዝቅ በማድረግና ማንነታቸውን በማለዘብ እርስ በርሳቸው መተናነሳቸው ግዴታ ነው።