ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እነዚያ ለሌሎች የሚያዝኑ አዛኙ ጌታ ሁሉን ነገር በሰፋው እዝነቱ እንደሚያዝንላቸው ገለፁ። ይህም ከሰሩት ጋር የገጠመ ምንዳ ነው። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ቀጥለው በምድር ላይ ለሚኖር ለሰውም፣ ለእንስሳም፣ ለበራሪም ሆነ ለሌላ ማንኛውም አይነት ፍጡር ባጠቃላይ ማዘንን አዘዙ። የዚህ ምንዳም ከሰማያቱ በላይ ያለው የአላህን እዝነት ማግኘት ነው።