ከዐብደላህ ቢን ዐምር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሉ: "ለአዛኞች አዛኙ ጌታ ያዝንላቸዋል። ለምድር ነዋሪዎች እዘኑላቸው በሰማይ ያለው (አላህ) ያዝንላቹሀል።" ሶሒሕ ነው። - አቡዳውድ፣ ቲርሚዚና አሕመድ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እነዚያ ለሌሎች የሚያዝኑ አዛኙ ጌታ ሁሉን ነገር በሰፋው እዝነቱ እንደሚያዝንላቸው ገለፁ። ይህም ከሰሩት ጋር የገጠመ ምንዳ ነው። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ቀጥለው በምድር ላይ ለሚኖር ለሰውም፣ ለእንስሳም፣ ለበራሪም ሆነ ለሌላ ማንኛውም አይነት ፍጡር ባጠቃላይ ማዘንን አዘዙ። የዚህ ምንዳም ከሰማያቱ በላይ ያለው የአላህን እዝነት ማግኘት ነው።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • የእስልምና ሀይማኖት የእዝነት ሀይማኖት ነው። የኢስላም ሁለመናው አላህን በመታዘዝና ለፍጡራን መልካም በማድረግ ላይ የቆመ ነው።
  • የላቀው አላህ በእዝነት ባህሪ የሚገለፅ ነው። ጥራት የተገባው አላህ አዛኝ ሩህሩህ ነው። ወደ ባሮቹ እዝነቱን የሚያደርስ ጌታ ነው።
  • ምንዳ የሚመነዳው በስራው አይነት ነውና ለአዛኞች አላህ ያዝንላቸዋል።