ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል: "የላቀውና ከፍ ያለው ጌታችን በሁሉም ሌሊት የመጨረሻ ሲሶ ሲቀር ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ይወርዳል። እንዲህም ይላል 'ማን ነው የሚለምነኝ የምመልስለት? ማን ነው የሚጠይቀኝ ለርሱ የምሰጠው? ማን ነው ምህረትን ከኔ የሚፈልገው ለርሱ የምምረው?'" ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

የጠራውና ከፍ ያለው አላህ በሁሉም ሌሊት የሌሊቱ የመጨረሻ ሲሶ ሲቀር ወደ ቅርቢቱ ሰማይ በመውረድ እርሱ ለለመነው ተቀባይ ለጠየቀው ሰጪ ነውና ባሮቹ እንዲለምኑት እንደሚያነሳሳ፤ የሚፈልጉትን እንዲጠይቁት እንደሚያነሳሳ፤ እርሱ ለአማኝ ባሮቹ መሀሪ ነውና ለወንጀሎቻቸውም ከርሱ ምህረትን እንዲፈልጉ እንደሚያበረታታቸው ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም ገለፁ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • የሌሊቱ የመጨረሻው ሲሶ ትሩፋቱንና በዚህ ወቅት ሶላት መስገድ ፣ ዱዓእ ማድረግና ምህረትን መፈለግ ያለውን ደረጃ እንረዳለን።
  • አንድ ሰው ይህንን ሐዲሥ በሚሰማበት ጊዜ ዱዓእ ተቀባይነት የሚገኝበት ወቅትን በመሸመት ላይ እጅግ የሚጓጓ ሊሆን ይገባል።