ከአቡ ሙሳ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል: 'አላህ በዳይን ያዘገየዋል። የያዘው ጊዜ ግን አይለቀውም!'" አቡ ሙሳ እንዲህ አለ: "ቀጥለውም {የጌታህም ቅጣት የከተሞችን ሰዎች እነሱ በዳዮች ሲሆኑ በቀጣቸው ጊዜ እንደዚህ ነው። ቅጣቱ በእርግጥ አሳማሚ ብርቱ ነው።} [ሁድ: 102] የሚለውን አነበቡ።" ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በወንጀል፣ በሽርክና ሰዎችን በመብታቸው በመበደል ላይ ከመዘውተር አስጠነቀቁ። ምክንያቱም አላህ በዳይን ያዘገየዋል፣ ያቆየዋል ፣ እድሜውንና ገንዘቡንም ያረዝምለታል። በቅጣትም አያቻኩለውም። ካልቶበተ ግፉ ስለበዛ ይይዘዋል አይለቀውምም አይተወውምም። ቀጥለውም ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም {የጌታህም ቅጣት የከተሞችን ሰዎች እነሱ በዳዮች ሲሆኑ በቀጣቸው ጊዜ እንደዚህ ነው። ቅጣቱ በእርግጥ አሳማሚ ብርቱ ነው።} [ሁድ: 102] የሚለውን አነበቡ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • አስተዋይ የሆነ ሰው ወደ ተውበት መቻኮል ይገባዋል። በበደል ላይ የዘወተረ ጊዜ አላህ አዘናግቶ እንደሚይዘው መጠራጠር የለበትም።
  • አላህ በዳዮችን ማዘግየቱና እነሱን በመቅጣት አለመቻኮሉ እነሱን ማዘናጊያና ካልቶበቱ ቅጣታቸውን ማነባበርያ ነው።
  • ግፍ የአላህን ቅጣት ህዝቦች ላይ የሚያመጣ አንዱ ምክንያት ነው።
  • አላህ አንድን መንደር ሲያጠፋ በውስጧ ደጋጎችም ሊኖሩ ይችላሉ። እነዚህ ደጋጎች የትንሳኤ ቀን በሞቱበት መልካምነት ላይ ሆነው ነው የሚቀሰቀሱት። ምድራዊ ቅጣቱ እነሱንም ማካተቱ በመጪው አለም አይጎዳቸውም።