explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሆን ብሎ ንግግርን ወይም ድርጊትን ወደርሳቸው አስጠግቶ በርሳቸው ላይ የዋሸ ሰው በመጨረሻው ዓለም በርሳቸው ላይ ለመዋሸቱ ምንዳ የእሳት መቀመጫ እንዳለው ገለፁ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • በነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ላይ አውቆና ሆን ብሎ መዋሸት እሳት ለመግባት ምክንያት እንደሆነ እንረዳለን።
  • በነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ላይ መዋሸትን ተከትሎ ከሚመጣው ዱንያዊና ሃይማኖታዊ ብልሽት ከባድነት አንፃር እርሳቸው ላይ መዋሸት በሌሎች ሰዎች ላይ እንደመዋሸት እንዳልሆነ እንረዳለን።
  • ሐዲሦች በትክክል ከነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መነገራቸውን ሳናረጋግግጥ በፊት ማሰራጨት መከልከሉን እንረዳለን።