ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አላህ የትንሳኤ ቀን ለሒሳብ ብሎ የመጀመሪያዎቹንም የመጨረሻዎቹንም የሰበሰበ ጊዜ ከአላህ ጋር ወይም ከሰዎች ጋር ሊሞላው ቃል የገባውን ቃል ኪዳን ላልሞላ ከዳተኛ ሁሉ ከዳተኝነቱ የሚጋለጥበት አርማ ይተከላል። በዛን እለትም በአርማው ላይ እንዲህ ተብሎ ይለፈፋል: "ይህ እከሌ የእከሌ ልጅ የከዳው ክዳት ነው።" ይህም የትንሳኤ ቀን ለተሰበሰቡ ሰዎች መጥፎ ስራውን ለማሳየት ነው።