ነቢዩ ( የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የተዋጊዎች አላማ ስለመለያየት ተጠየቁ። ለጀግንነት ወይም ለወገንተኝነት ወይም ደረጃው ሰው ዘንድ እንዲታይለት ወይም ከዚህ ውጪ ላለ አላማም ከተጋደለ ሰው መካከል በአላህ መንገድ ተጋደለ የሚባለው ማንኛው ነው? ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በአላህ መንገድ የሚጋደል የሚባለው ሰው የአላህ ቃል የበላይ እንድትሆን የተጋደለ ሰው መሆኑን ተናገሩ።