ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል: "በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካምን ይናገር ወይም ዝም ይበል! በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ ጎረቤቱን ያክብር! በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ እንግዳውን ያክብር!" ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በአላህ እና በሚመለስበትና በስራው የሚመነዳበት በሆነው በመጨረሻው ቀን ያመነ ባሪያ ኢማኑ እነዚህን ጉዳዮችን በመፈፀም ላይ እንደሚያነሳሳው ገለፁ: የመጀመሪያው: መልካም መናገር ነው። በዚህ ውስጥ ሱብሓነላህ ማለት፣ ላኢላሃኢለላህ ማለት፣ በመልካም ማዘዝ፣ ከመጥፎ መከልከል፣ በተጣሉ ሰዎች መካከል ማስማማት የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ። ይህንን ካልፈፀመ ዝምታን ያዘውትር፣ ክፋቱን ይቆጥብ፣ ምላሱን ይጠብቅ። ሁለተኛ: ጉረቤትን ማክበር፡ ይህም እነሱን ባለማወክና ለነርሱ በጎ በማድረግ ነው። ሶስተኛ: ለመዘየር የመጣን እንግዳ መልካም በማናገር፣ ምግብ በማብላትና ይህን በመሳሰሉት ማክበር ነው።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • በአላህና በመጨረሻው ቀን ማመን ለሁሉም መልካም ነገር መሰረት ነው። መልካም ተግባራትን በመፈፀም ላይም ያነሳሳል።
  • ከምላስ ወለምታ መከልከሉን እንረዳለን።
  • የኢስላም ሃይማኖት የአንድነትና የቸርነት ሃይማኖት መሆኑን እንረዳለን።
  • እነዚህ ጉዳዮች ከኢማን ክፍሎችና ምስጉን ከሆኑ ስነስርአቶች መካከል መሆናቸውን እንረዳለን።
  • ንግግር ማብዛት ወደሚጠላ ወይም ወደተከለከለ ነገር ይጎትታል። ሰላም የሚገኘው ከመልካም ውጪ ባለመናገር እንደሆነ እንረዳለን።