ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አላህ ዘንድ ተወዳጅ ንግግሮች አራት መሆናቸውን ተናገሩ: "ሱብሓነላህ": ማለትም አላህን ከሁሉም ጉድለት ማጥራት ነው። "አልሐምዱ ሊላህ": አላህን ከመውደድና ከማላቅ ጋር በምሉዕነት ባህሪ መግለፅ ነው። "ላኢላሃ ኢለላህ": ማለትም ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። "አላሁ አክበር": ማለትም አላህ ከሁሉም ነገር የበለጠ ታላቅና ሀያል ነው። ትሩፋቷንና ምንዳዋን ለማግኘት የቃላቱን ቅደም ተከተል መጠበቅ ግዴታ አይደለም።