ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) አላህን ከማውሳት ከመዘናጋት አስጠነቀቁ። እርሱም ሰዎች አላህን በርሱ ያላወሱበትና በመልክተኛው (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ላይ ሶላት ያላወረዱበት መቀማመጥ ከተቀመጡ ይህ መቀማመጥ የትንሳኤ ቀን በነርሱ ላይ ቁጭት፣ ፀፀት፣ ክስረትና ጉድለት ይሆንባቸዋል። ከፈለገ አላህ በቀደመ ወንጀላቸውና ባለባቸው ጉድለት ምክንያት ይቀጣቸዋል። ከፈለገም በችሮታውና በእዝነቱ ለነርሱ ይምራቸዋል።