ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) (ረዲቱ ቢላሂ ረብበን) በአላህ አምላክነት፣ ተንከባካቢነት፣ ንጉስነት፣ አለቃነት፣ አስተካካይነት ወድጃለሁ፤ (ወቢልኢስላሚ) በእስልምና በሁሉም ትእዛዛዊና ክልከላዊ ህግጋቶቹ (ዲነን) መንገድነት፣ ሃይማኖትነትና እምነትነት ወድጃለሁ፤ (ወቢሙሐመደን ረሱላ) በሙሐመድ ነቢይነት፣ እርሳቸው በተላኩበትና ወደኛ ባደረሱት ነገር ሁሉ ወድጃለሁ ያለ ሰው ጀነት ለርሱ እንደፀናችለት ተናገሩ።