ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለሶላት ተክቢራ ያደረጉ ጊዜ ፋቲሓ ከመቅራታቸው በፊት ትንሽ ዝም ይሉ ነበር። በዚህ ዝም ባሉበት ወቅትም ሶላታቸውን በአንዳንድ ዱዓ ይከፍታሉ። ከነዚህ ከተላለፉልን ዱዓዎች መካከልም: "አልላሁምመ ባዒድ በይኒ ወበይነ ኸጧያየ ከማ ባዐድተ በይነል መሽሪቂ ወልመግሪብ አልላሁመ ነቂኒ ሚን ኸጧያየ ከማ ዩነቃ አሥሠውቡል አብየዱ ሚነደነስ፣ አልላሁመ ኢግሲልኒ ሚን ኸጧያየ ቢሥሠልጂ ወልማኢ ወልበረድ።" ሰውዬው በዚህ ዱዓ በምስራቅና ምዕራብ መካከል ፈፅሞ መገናኘት እንደማይኖረው ሁሉ ከርሱ ጋር በማይገናኙ መልኩ በርሱና በወንጀሎቹ መካከልም አላህ ዐዘ ወጀል እንዲያራርቅ እና ወንጀል ላይ እንዳይወድቅ፤ ወንጀል ላይ ከወደቀ እንኳ ነጭ ልብስ ከእድፍ እንደሚጠራው ከወንጀሉ እንዲያጠራውና እንዲያስወግድለት፣ ከወንጀሉ እንዲያጥበውና የወንጀሉን ሀሩርና ወላፈንንም በውሃ፣ በጤዛና በረዶ እንዲያቀዘቅዝለት ነው ዱዓ የሚያደርገው።