ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከስለት ከለከሉ። ይህም አንድ ሰው አላህ ግዴታ ያላደረገበትን ነገር በራሱ ላይ ግዴታ ማድረጉ ማለት ነው። እንዲህም አሉ: ስለት አንድን ነገር አያመጣምም አያዘገይምም። ከስለት የሚገኘው ግዴታ የሆነበትን ነገር ካልሆነ በቀር የማይፈፅምን የሆነ ስስታም ሰው ተገዶ እንዲያወጣ ማስድረጉ ነው። ስለት ያልተወሰነልህን ነገር አያመጣም።