ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አዛን ባይን በሚሰማ ጊዜ አዛኑን ካጠናቀቀ በኋላ እንዲህ የሚል ሰውን ገለፁ። (የዚህ የተሟላ ጥሪ ጌታ የሆንከው አላህ ሆይ!) የተሟላ ጥሪ የተባለው ወደ አላህ አምልኮና ወደ ሶላት የሚጠራበት የሆነው የአዛን ጥሪ ነው። (የተሟላ) ማለት መልዕክቱና የተውሒድ ጥሪው የተሟላ የሆነው ማለት ነው። (የቆመችው ሶላትም ጌታ) ማለት ዘውታሪ የሆነችው ሶላት ማለት ነው። (ለሙሐመድ ወሲላን ስጥ) ማለት ለነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ካልሆነ በቀር ለማንም የማትገባ የሆነችው ጀነት ውስጥ ያለች ከፍተኛዋን ደረጃ ስጣቸው፤ (ፈዲላንም) ማለት ከፍጡራን ደረጃዎች በላይ ከፍ ያለች ደረጃንም ስጣቸው። (ምስጉኑን ስፍራም ስጣቸው) ማለት እዛ ቦታ የቆመ ምስጉን የሚሆንበት ስፍራ ነው። እርሱም የትንሳኤ ቀን ያለው ትልቁ ምልጃ ነው። (ቃል የገባህላቸው የሆነውን) ማለት {ጌታህ ምስጉን በሆነ ስፍራ በእርግጥ ያቆምሃል።} በሚለው ቃልህ ለነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንድትሆን ቃል የገባኸውን ስፍራ ስጣቸው ማለት ነው። ይህን ዱዓ የለመነም ሰው የትንሳኤ ቀን የነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ምልጃ ይረጋገጥለታልም ይፀድቅለታልም።