አቡበከር አስሲዲቅ (ረዺየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ሰዎች ይህቺን አንቀፅ እንደሚያነቡ ተናገሩ: {እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነፍሶቻችሁን (ከእሳት) ያዙ! (ጠብቁ)። በተመራችሁ ጊዜ የተሳሳተ ሰው አይጎዳችሁም።} [አልማኢዳህ: 105] ከዚህም አንቀፅ የሰው ልጅ ያለበት ግዴታ ነፍሱን በማስተካከል ላይ መልፋት ብቻ እንደሆነ፤ ነፍሱን ካስተካከለም የጠመመ ቢጠም ምንም እንደማይጎዳቸው፣ በመልካም በማዘዝና ከመጥፎ በመከልከል ዙሪያ እንደማይጠየቁ ይረዳሉ። ይህ ግን (እነሱ እንዳሰቡት) አለመሆኑን ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ሲሉ እንደሰማቸው በመንገር አሳወቃቸው: ሰዎች ግፈኛን ተመልክተው በመከልከል ላይ አቅሙ እያላቸው ከግፉ ካልከለከሉት አላህ መጥፎውን የሰራውንም ሆነ አይቶ ዝም ያለውን ሁሉንም እርሱ ዘንድ ባለ ቅጣት ሊጠቀልላቸው ይቀርባል።