ከአቡ ሰዒድ አልኹድሪይ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፦ "ከናንተ መካከል እውነታን ተመልክቶ ወይም አውቆ ከመናገር ማናችሁንም ቢሆን ለሰዎች ያለው ፍራቻ እንዳይከለክለው።" ሶሒሕ ነው። - ቲርሚዚ፣ ኢብኑ ማጀህና አሕመድ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በባልደረቦቻቸው መካከል ኹጥባ አደረጉ። ከመከሯቸው ጉዳዮችም አንዱ የትኛውም ሙስሊም እውነትን ተመልክቶ ወይም አውቆ ከመናገርና በርሱ ከማዘዝ ሰዎችንና ሀይላቸውን መፍራትና መስጋት እንዳይከለክለው ነው።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • እውነትን ግልፅ በማድረግና ሰዎችን ፍራቻ እውነትን ባለመሸሸግ ዙሪያ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  • እውነትን መናገር ማለት በአነጋገር መንገዱ ስርአትን፣ ጥበብንና በመልካም መልኩ መገሰፅን አይተግብር ማለትን አያሲዝም።
  • መጥፎን ማውገዝና ከአላህ ሐቅ ጋር ከሚጋጭ የሰዎች ጥቅም የአላህን ሐቅ ማስቀደም ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።