ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የጀነት ነዋሪዎች በጀነት ውስጥ እየተጣቀሙ ሳሉ አንድ ተጣሪ እንዲህ በማለት እንደሚጣራ አወሱ "ጀነት ውስጥ ለናንተ ጤና አላችሁ መቼም ትንሽ እንኳ ብትሆን ህመም አትታመሙም። ለናንተ ህያውነት አላችሁ፤ ትንሿ ሞት የሆነችውን እንቅልፍ እንኳ ቢሆን መቼም ጀነት ውስጥ አትሞቱም። ለናንተ ወጣትነት አላችሁ፤ መቼም ጀነት ውስጥ አታረጁም። ለናንተ ጀነት ውስጥ መጣቀም አላችሁ፤ መቼም ጀነት ውስጥ አታዝኑምም አትቸገሩምም። ይህም ይህ የአላህ ዐዘ ወጀል ንግግር ነው: {ይህች ጀነት ትሰሩት በነበራችሁት ተሰጣችኋት በማለት ይጠራሉ።} [አልአዕራፍ: 43]