ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ለአቡ ሰዒድ አልኹድሪይ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - በአላህ ያመነና በጌትነቱ፣ በአምላክነቱ፣ በንጉስነቱ፣ በአለቃነቱ በአዛዥነቱ የወደደ፤ በእስልምና ሃይማኖትነት የወደደና በአጠቃላይ ትእዛዛቶችና ክልከላዎቹ የተመራና እጅ የሰጠ፤ በሙሐመድ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ነቢይነትና ይዘውት በመጡትና ባደረሱት ነገር ሁሉ የወደደ ሰው ጀነት ለርሱ ፀንታለታለች አሉት። አቡ ሰዒድም (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - በዚህች ንግግር በመደሰት "ድገሙልኝ የአላህ መልክተኛ" አላቸው። ነቢዩም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ደገሙለትና አክለውም እንዲህ አሉት: "እኔ ዘንድ ሌላ ጉዳይ አለች። አንድ ባሪያ በርሷ ሰበብ ጀነት ውስጥ መቶ ደረጃ ከፍ የሚደረግባት የሆነች፤ በየሁሉም ደረጃ መካከል ያለው ርቀትም በሰማይና በምድር መካከል እንዳለው ርቀት ነው።" አቡ ሰዒድም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ምንድናት እርሷ?" አለ። እርሳቸውም "በአላህ መንገድ መታገል! በአላህ መንገድ መታገል!" አሉት።