ከዐብደላህ ቢን ዐምር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው:- "አንድ ሰውዬ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) 'ማንኛው የኢስላም ክፍል ነው ምርጡ?' ብሎ ጠየቀ። እርሳቸውም 'ምግብ መመገብህ፣ ሰላምታን ባወቅከውም ባላወቅከውም ሰው ላይ ማቅረብህ ነው።' ብለው መለሱለት።" ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ማንኛው የኢስላም ክፍል ነው በላጩ? ተብለው ተጠየቁ። እርሳቸውም ሁለት ነገሮችን ጠቀሱ። የመጀመሪያው: ድሃዎችን ማብላትን ማብዛት ነው። እዚህ ውስጥም ሶደቃ፣ ስጦታ፣ ግብዣ፣ የሰርግ ድግስ ይገባሉ። የማብላቱ በላጭነትም በረሃብና ኑሮ በተወደደበት ወቅት የጠነከረ ይሆናል። ሁለተኛው: አወቅከውም አላወቅከውም በሁሉም ሙስሊም ላይ ሰላምታን ማቅረብ ነው።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ሶሐቦች በዱንያም ሆነ በመጨረሻው ዓለም የሚጠቅምን ጉዳይ ለማወቅ ያላቸውን ጉጉት እንረዳለን።
  • ሰላምታ ማቅረብና ምግብ ማብላት ሰዎች በሁሉም ወቅት የሚፈልጉት ስለሆነና በላጭ ስራ ከመሆኑ አንፃር በኢስላም ውስጥ ትልቅ ደረጃ ከሚሰጣቸው ተግባራት መካከል እንደሆኑ እንረዳለን።
  • በነዚህ ሁለት ጉዳዮች ንግግራዊም ተግባራዊም በጎነት ይሰበሰባሉ። ይህም የተሟላው በጎነት ነው።
  • እነዚህ ጉዳዮች ሙስሊሞች በመካከላቸው ሊኖራቸው ከሚገባው መስተጋብር ጋር የተያያዘ ሲሆን ሌላ ቦታ ደግሞ አንድ ባሪያ ከጌታው ጋር ሊኖረው ስለሚገባ መስተጋብር የሚገልፁ ጉዳዮች አሉ።
  • በሰላምታ መጀመር በሙስሊሞች መካከል ብቻ የተገደበ ሲሆን ካፊር በሰላምታ አይጀመርም።