ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለወንጀሎቻቸው መማር፣ ከጠባቂ መልአክት መዝገብ ወንጀላቸውን ለማሰረዝ፣ በጀነት ውስጥም ደረጃዎችን ከፍ ለማድረግ ምክንያት የሚሆኑ ስራዎችን እንዲጠቁሟቸው ይፈልጉ እንደሆነ ባልደረቦቻቸውን ጠየቋቸው። ሶሐቦችም: "አዎን እንፈልጋለን" አሉ። እሳቸውም እንዲህ አሉ: የመጀመሪያው: እንደ ቅዝቃዜ፣ የውሃ ማነስ፣ የሰውነት ህመምና አቃጣይ ውሃን የመሰሉ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙም ዉዱእን መሙላትና ማዳረስ ነው። ሁለተኛው: ከሩቅ አካባቢ በመነሳት ወደ መስጂድ እርምጃን ማብዛትና ደጋግሞ መመላለስ ነው። ሶስተኛ: የሶላትን ወቅት መጠበቅ፣ ልብን በሶላት ማንጠልጠል፣ ለሶላት መዘጋጀት፣ ጀመዓን ለመጠበቅ መስጂድ ውስጥ ለሶላት መቀመጥ፣ ከሰገደም በኋላ ለሌላ ሶላት መስገጃው ላይ ቁጭ ብሎ መጠበቅ ነው። ቀጥለው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እነዚህ ጉዳዮች ትክክለኛው ዘብ መጠበቅ እንደሆኑ ገለፁ። ምክንያቱም የሰይጣንን መንገዶች በነፍስ ላይ ስለምትዘጋ፣ ስሜትን ስለምታሸንፍ፣ ነፍስ ለወስዋስ ተገዥ እንዳትሆን ስለምትከለክል ነው። ነፍስን በማሸነፍ የአላህ ጭፍራ የሰይጣንን ሰራዊት ያሸንፉበታል። ትልቁ ጂሀድም ይህ ነው። ስለዚህ የዚህ ደረጃ ኬላ ላይ ጠላትን እንደመጠበቅ እንደሆነ አድርገው ገለፁት።