ራፊዕ ቢን ኸዲጅ ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - በዙል ሑለይፋ ከነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ጋር እንደነበር ተናገረ። ሰዎችንም ረሃብ አጋጠማቸው። ከአጋርያን የማረኩት ፍየሎችና ግመሎች ነበሩ። ነቢዩን ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሳያስፈቅዱም ምርኮ ከመከፋፈሉ በፊት ቸኮሉና አረዱ። ድስጥ ላይም ጣዱት። ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ከሰዎች ኋላ ነበሩ። ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ያደረጉትን ሲያውቁ ድስጧ እንድትደፋ አዘው ከነመረቁ አስደፉት። ቀጥለው ምርኮዉን አከፋፈሉ። አስር ፍየሎችን በአንድ ግመል ተለዋጭ እያደረጉ አከፋፈሉ። ከነዚህ ግመሎችም አንድ ግመል ሸሸ። የነበራቸው ፈረስ ትንሽ ነበረና እርሱ ላይ መድረስ አቃታቸው። ከመካከላቸው የነበረ አንድ ሰውዬም በቀስት ወጋው። አላህም አቆመላቸው። ነቢዩም ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ አሉ: "እነዚህ ለማዳ እንስሶችም የዱር ባህሪ አላቸው። ከነርሱ መካከል ለመያዝ ያቃታችሁና ያሸነፋችሁን እንደዚሁ አድርጉት።" ራፊዕም እንዲህ አለ: "እኛ ነገ ጠላትን እንገናኛለን ብለን ተስፋ እናደርጋለን። በመሳሪያዎቻችን እንዳናርድ ስለቱን እንዳይጎዳብን ያሰጋናል። ማረዳችን ደግሞ ግድ ነው። እኛ ጋር ደግሞ ቢላ የለንምና በደረቀ ስለታማ ቀርከሃ እንረድን?" ነቢዩም ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- "ከጥርስና ከጥፍር ውጪ ደምን አብዝቶ ያፈሰሰና ሲታረድ የአላህ ስም የተወሳበትን ብሉ። የሁለቱንም ምክንያት እነግራችኋለሁ። ጥርስ የማታርዱበት አጥንት ስለሆነ ነው። ጥፍር የማታርዱበት ደግሞ የሐበሻ ከሃዲዎች ለማረድ የሚጠቀሙበት ስለሆነ ነው።" አሉ።