explain-icon

ትንታኔ

ሰውዬው እንደሚስቱ፣ ወላጆቹ፣ ልጁና ሌሎችንም እነርሱ ላይ ወጪ ማውጣት ግዴታ ለሆነበት አካል ሲሰጥ ወደ አላህ መቃረብንና አላህ ዘንድ ምንዳን እያሰበ ከሆነ ለርሱ የምፅዋት ምንዳ እንደሚሰጠው ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ተናገሩ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ለቤተሰቦች ወጪ በማውጣት ምንዳና አጅር እንደሚገኝ እንረዳለን።
  • ሙእሚን የሆነ ሰው በስራው የአላህን ፊትና እርሱ ዘንድ ያለውን ምንዳና አጅር እንደሚፈልግ እንረዳለን።
  • በሁሉም ስራዎች መልካምን ኒያ ማድረግ ይገባል። ከነዚህም ስራዎች መካከል ለቤተሰቦች ወጪ በምናወጣ ጊዜ አንዱ ነው።