ከዐብደላህ ቢን ዑመር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ - የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ሚንበር ላይ ሳሉ ስለ ምፅዋት፣ ጥብቅነትና ልመና ካወሱ በኋላ እንዲህ አሉ: "ከላይ ያለች እጅ ከታች ካለች እጅ የተሻለች ናት። ከላይ ያለች እጅ ሰጪዋ ስትሆን ከታች ደግሞ ጠያቂዋ እጅ ናት።"» ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።