explain-icon

ትንታኔ

ከፍ ያለውና የላቀው አላህ "የአደም ልጅ ሆይ! ግዴታም ይሁን ተወዳጅ የሆኑብህን ወጪዎች ለግስ! ላንተም ሲሳይን አሰፋልሃለሁ፣ ያወጣኸውን ወጪ ልውጫ እሰጥሃለሁ፣ በሰጠሁህም ነገር ላንተ እባርክልሃለሁ" ማለቱን ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ተናገሩ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • በአላህ መንገድ መስጠትና መመፅወት መበረታታቱን እንረዳለን።
  • መልካም በሆኑ መንገዶች ላይ ወጪ ማድረግ ሲሳያችን በረከት እንዲያገኝና እንዲባዛ ከሚያደርጉ እንዲሁም ሰውዬው ያወጣውን ወጪ አላህ እንዲተካለት ከሚያደርጉ ትልልቅ ምክንያቶች መካከል ነው።
  • ይህ ሐዲሥ ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከጌታቸው ከሚያስተላልፉት ሐዲሥ መካከል አንዱ ነው። ሐዲሠል ቁድሲይ ወይም ሐዲሠል ኢላሂይ በመባል ይጠራል። ቃሉም ሀሳቡም ከአላህ ሲሆን ነገር ግን ቁርአን ከሌሎች የተለየበት የሆኑ በማንበቡ (በየፊደላቱ ሐሰና የሚያስገኘውን) አምልኮን መፈፀም፣ እሱን ለማንበብ ውዱእ ማድረግና አምሳያውን ማንም እንደማያመጣ መነገሩ፣ ተአምራዊነቱና ከዚህም ውጪ ያሉ የቁርአን መለዮዎችን አልያዘም።