ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ለወደፊት ስለሚከሰቱ የሩቅ ሚስጥራት ስለሚናገሩ ሰዎች ተጠየቁ። እሳቸውም: ቦታ አትስጡት ፤ ንግግራቸውን አትያዙ፤ ጉዳያቸው አያሳስባችሁ አሉዋቸው። ሶሐቦችም "በእንዲህ ወርና በእንዲህ ቀን" ብለው የሩቅ ሚስጥር ጉዳይ እንደሚከሰት እንደሚናገሩና እንደተናገሩት ገጥሞ መከሰቱን አይነት ንግግራቸው አንዳንድ ጊዜ ተጨባጩን የሚገጥም መሆኑን ተናገሩ። ነቢዩም ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለምም እንዲህ ብለው መለሱላቸው "ጂኖች ከሰማይ የሚሰሙትን ወሬ በመስረቅ ወደ ጠንቋይ ወዳጆቻቸው አውርደው የሰሙትን ይነግሯቸዋል። ከዚያም ጠንቋዩ ከሰማይ በሰማው ላይ መቶ ውሸት ይጨምርበታል።"