ከሳሊም ቢን አቢ ጀዕድ እንደተዘገበው እንዲህ አሉ: "አንድ ሰውዬ እንዲህ አለ: 'ምናለ ሰግጄ እረፍት ባገኘሁ።' አለ። ሰዎቹ በዚህ ንግግሩ ላይ ያነወሩት መስሎ ሲታይም እንዲህ አለ: 'የአላህን መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ: ‹ቢላል ሆይ! ሶላትን ኢቃም ብለህ በሶላት እረፍት ስጠን።›'" ሶሒሕ ነው። - አቡዳውድ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ከሶሐቦች መካከል አንዱ "ምናለ ሰግጄ እረፍት ባገኘሁ።" አለ። በዙሪያው ያሉ ሰዎች በዚህ ንግግሩ ላይ ያነወሩት መሰሉ። በዚህ ጊዜም እንዲህ አለ: "ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ: 'ቢላል ሆይ! የሶላትን አዛንና ኢቃም አድርግ በርሷ እረፍት እንድናገኝ!'" ይህም ሶላት ውስጡ አላህን ማናገር፣ ለነፍስና ለቀልብ እርካታ ስላለው ነው።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ሶላት ውስጥ አላህን ማናገር ስላለ የቀልብ እርካታ የሚገኘው በሶላት ነው።
  • አምልኮ መፈፀም በከበደው ላይ መወገዙን እንረዳለን።
  • ያለበትን ግዴታ የተወጣና ጫንቃውን ካለበት ግዴታ ያጠራ በዚህ እርካታና የእረፍት ስሜትን ያገኛል።