ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ፀሐይ በምትወጣበት ቀናት ሁሉ ሁለት መልአኮች ወርደው እንደሚጣሩ ተናገሩ። አንደኛቸው እንዲህ ይላል: አላህ ሆይ! አላህን ለመታዘዝ፣ ለቤተሰቦቹ፣ ለእንግዶቹ፣ ለበጎ አድራጎት ለሚሰጥ ሰው ምትኩን ስጠው፤ ካወጠው የተሻለ ተካለትም ባርክለትም። ሌላኛው ደግሞ "አላህ ሆይ! ከመስጠት የሚቋጥርን ጥፋትን ስጠው፤ ለሚገባቸው ከመስጠት ገንዘቡን የነፈገንም ገንዘቡን አውድምበት!" ይላል።