ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን የትንሳኤ ቀን ከኡመታቸው መካከል ወደ ኩሬያቸው የሚመጣን ሰው ለመመልከት ከኩሬያቸው ላይ እንደሚሆኑ ገለፁ። ከሳቸው አቅራቢያም ሰዎች እንዳይጠጡ ይያዛል። እርሳቸውም፦ "ጌታዬ ሆይ እነሱ ከኔ ኡመት እኮ ናቸው" ይላሉ። ለርሳቸውም፦ "አንተን ከተለያዩ በኋላ የሰሩትን ታውቃለህን? በአላህ እምላለሁ ወደኋላቸው ከመመለስና ከእምነታቸው ከማፈንገጥ አልተወገዱም። ከአንተም አይደሉም ከኡመትህም አይደሉም።" ተብሎ ይመለስላቸዋል።