ከዐብደላህ ቢን መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል: "ጉንጩን የመታ፣ አንገትያውን የቀደደ፣ በድንቁርና ጥሪ የተጣራ ከኛ አይደለም።"» ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከአንዳንድ የድንቁርና ዘመን ሰዎች ተግባር አስጠነቀቁም ከለከሉም። እንዲህም አሉ: እነዚህ ከኛ አይደሉም: የመጀመሪያው: ጉንጩን የመታ ነው። ጉንጭን የለዩት በአብዛኛው የሚፈፀመው እርሱ ስለሆነ ነው እንጂ የተቀሩትን የፊት ክፍልን መምታትም ክልከላው ውስጥ ይካተታል። ሁለተኛው: ልብስ ላይ ጭንቅላት እንዲገባበት ተብሎ የሚከፈተውን (አንገትያ) ከትእግስት ማጣት ብዛት መቅደድ ነው። ሶስተኛው: የድንቁርና ዘመን ጥሪዎችን መጣራት ነው። ለምሳሌ ያህል፦ ወዮልኝ፣ ወይኔ በጠፋው ማለት፣ ሙሾ ማውረድ፣ እየገጠሙ ማለቃቀስና ሌሎችም ይጠቀሳሉ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ሐዲሡ ውስጥ የመጣው ይህ (ከእኛ አይደሉም የሚለው) ዛቻ እነዚህ ተግባራት ከትላልቅ ወንጀሎች መካከል መሆናቸውን ይጠቁማል።
  • በመከራ ላይ መታገስ ግዴታ መሆኑንና አሳማሚ በሆኑ የአላህ ውሳኔዎች ላይ መበሳጨት ክልክል መሆኑን እንረዳለን። የዚህም መገለጫው: ሙሾ በማውረድ ወይም እየገጣጠሙ በማልቀስ ወይም በመላጨት ወይም በመቀዳደድ ወይም ከዚህም ውጪ ያለን በመስራት ነው።
  • ሸሪዓ ያላፀደቀውን የድንቁርና ዘመን ጉዳዮችን መከተል ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  • ማዘንና ማልቀስ በአላህ ውሳኔ ላይ ከመታገስ ጋር ስለማይፃረር ችግር የለውም። ማልቀስ አላህ በቅርብ ዘመዶችና ወዳጆች ቀልብ ውስጥ ያደረጋት እዝነት ናት።
  • ሙስሊም የሆነ ሰው በአላህ ፍርድ መውደድ አለበት። ባይወድ እንኳን መታገስ ግዴታው ነው።