ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከርሳቸው በፊት አላህ በህዝቦች ውስጥ የላከው እያንዳንዱ ነቢይ ከህዝቦቹ መካከል የተመረጡ፣ ረዳቶች፣ ታጋዮች፣ ታማኞች፣ ከርሱ በኋላ ለተተኪነት የሚበጁ፣ ፈለጉን የሚይዙና ትእዛዙንም የሚከተሉ ባልደረቦች ይኖሩታል፤ ከዚያም ከነዚህ መልካም አበዎች በኋላ ግን ምንም መልካም የሌላቸው የማይሰሩትን የሚናገሩና ያልታዘዙትን የሚሰሩ ሰዎች ይመጣሉ። በእጁ የታገላቸው እርሱ አማኝ ነው። በምላሱ የታገላቸው እርሱም አማኝ ነው። በቀልቡም የታገላቸው እርሱ አማኝ ነው። ከዚህ ውጪ የሆነ ሰው ግን የጎመንዘር ፍሬ ያህል እንኳ ኢማን እንደሌለው ተናገሩ።