explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከርሳቸው የተማርነውን ቁርአናዊም ይሁን ሐዲሣዊ እውቀት አንድ አንቀፅ ያህል ትንሽ እንኳ ቢሆን እንድናስተላልፈው አዘዙን፤ ይህም ግን የምንጣራበትንና የምናደርሰውን መልእክት ተረድተነው መሆኑ ቅድመ መስፈርቱ ነው። ከዚያም ሽሪዓችን ጋር እስካልተጋጨ ድረስ ከበኒ ኢስራኢሎች የተከሰተባቸውን ክስተትና መሰል ጉዳዮችን በተመለከተ ማውራታችንም ችግር እንደሌለው ገለፁ። ከዚያም በሳቸው ላይ ከመቅጠፍ አስጠነቀቁ፤ ሆን ብሎ በሳቸው ላይ የዋሸም ጀሀነም ውስጥ ማረፊያውን እንዲይዝ አሳሰቡ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • የአላህን ሸሪዓ ማስተላለፍ እንደሚበረታታና ማንኛውም ሰው የሸመደደውና የተረዳውን ትንሽም ቢሆን ማድረስ እንዳለበት እንረዳለን።
  • አሏህን በትክክል ለማምለክና መልዕክቱንም ለማድረስ እንዲያስችል ሸሪዓዊ እውቀትን መፈለግ ግዴታ ነው።
  • ይህ ከባድ ዛቻ ከሚመለከታቸው ሰዎች ላለመሆን ሲባል የትኛውንም ሐዲሥ ከማስተላለፋችንና ከማሰራጨታችን በፊት በትክክል ከሳቸው መሆኑን ማረጋገጥ ግዴታ ነው።
  • ውሸት ላይ ላለመውደቅ ሲባል በተለይም በአሏህ ሸሪዓ ላይ በንግግራችን እውነተኞችና የምናወራውም የተሟላ መረጃ ያለንን ጉዳይ መሆኑ እንደሚበረታታ እንረዳለን።